Miheret.com
  • Home
  • Blog
  • Give
  • About

እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገልን ደስም አለን

7/8/2018

 
Picture
ካለፉት ሁለት ሳምንታት ጀምሮ ይህ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል በዓይምሮዬ ሲመላለስ ነበር። ክፍሉም የመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ምዕራፍ 126 ሲሆን እንዲህ ይላል፣
1  እግዚአብሔር የጽዮንን ምርኮ በመለሰ ጊዜ፣
ሕልም እንጂ እውን አልመሰለንም።
2በዚያን ጊዜ አፋችን በሣቅ፣
እንደበታችንም በእልልታ ተሞላ፤
በዚያን ጊዜም በሕዝቦች መካከል፣
“እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገላቸው” ተባለ።
3 እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አደረገልን፤
እኛም ደስ አለን።
4 እግዚአብሔር ሆይ፤ በነጌቭ እንዳሉ ጅረቶች፣
ምርኳችንን መልስ።
5በእንባ የሚዘሩ፣
በእልልታ ያጭዳሉ።
6ዘር ቋጥረው፣
እያለቀሱ የተሰማሩ፣
ነዶአቸውን ተሸክመው፣
እልል እያሉ ይመለሳሉ።
አንዳንድ የመፅሐፍ ቅዱስ አዋቂዎች ይህ ዝማሬ እስራኤላውያን ከምርኮ በተመለሱ ጊዜ የተዘመረ እንደሆነ ይናገራሉ።  በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ዝማሬ ንጉስ ዳዊት ልጁ አቤሴሎም በትረ ስልጣኑን በጉልበት ለመውሰድ በሞከረበት ጊዜ ሸሽቶ ከነበረበት ስፍራ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ የተዘመረ መዝሙር እንደ ሆነም የሚፅፉ አሉ። እናም የግጥሙ ፀሃፊ የደስታውን ሁኔታ በቁጥር አንድ ላይ "ህልም እንጂ እውን አልመሰለንም" ብሎ ይገልፀዋል። ይህም የእርስ በእርስ ዕልቂት፣ የጦርነት እና የምርኮ ስብራት ቶሎ የማይጠገን መሆኑን የሚጠቁም ነው።
​

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ እየሆነ ያለውን መንፈሳዊ፤ፖለቲካዊ እና ፈረጀ ብዙ ተሃድሶ ህልም እንጂ እውን አይመስልም ያስብላል። የአሜሪካው ድምፅ ጋዘጠኛ ሰለሞን የዞን ዘጠኝ ጦማሪ አባል እና የሰብአዊ መብት አክቲቪስት የሆነችውን ሶልያናን በአንድ ዲስያፖራ ስብሰባ ላይ (10ኛ ደቂቃ ላይ ማየት ይችላሉ) በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት እየሆነ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ ጥያቄ ሲጠይቃት የመለሰችው መልስ “እያየን ያለነው ለውጥ ትንሽ ፈጣን ናቸው። ለመከታተልም ይከብዳል” የሚል ነበር። ሶልያና በብዙ የፍትህ ማጣት ችግር ያለፈች በመሆኗ አሁን እያየን ያለውን  ሁኔታ የገለፀቸበት መንገድ ማጋነን አይሆንባትም። ምክንያቱም እንዳለችው እየሆነ ያለው ለውጥ እጅግ ፈጣን እና ለማመን ህልም የሚመስል ነው በመሆኑ ነው።

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦርነት ውስጥ ከገቡበት ጊዜ እንስቶ ሁለቱም ህዝቦች አልቅሰዋል፤ለስደት ተዳርገዋል፤ ብሎም በሺዎች ሞተዋል። እኔም የማስታውሳቸው የጎረቤት ቤተሰብ ተለያይተዋል። ባል ኤርትራዊ፣ ሚስት ደሞ ኢትዮጵያዊ ሰለሆነች በጦርነቱ ጊዜ ባል እና ሚስት ተለያይተው እንዲኖሩ ምክንያት ሆኗል፤ ልጆቻቸውም እንዲሁ።

ታዲያ በዚህ መራራ ታሪክ ውስጥ ብዙ ሲፀለይ ቆይቷል። እግዚአብሔርም ፀሎትን መልሷል። እንባም ታብሷል።  አዲስ የሰላም ምዕራፍ ተከፍቷል። ይህ አዲስ መንፈስ በሁለቱም ሀገሮች ላይ እየነፈሰ ነው። ለዚህ ማሳያ በአስመራ ጠ/ሚ ዐብይ አህመድን ሊቀበል የወጣው ህዝብ ምስክር ነው።
የሚገባኝ ይህ ደስታ ዋጋ የተከፈለበት ደስታ መሆኑን ነው። ይህ በሀገር ላይ የፈሰሰው ደስታ ለብዙ ወጣቶች ስኬት መስፈንጠሪያ እንድሚሆን ምንም ጥርጥር የለኝም። በዚህ ደስታ ውስጥ ዐይኑ የተከፈተለት ብዙ ዕድሎችን ማየት ይችላል።   ስለዕድሎቹ ሌላ ጊዜ እመለሳለሁ። በተፈጠረው የደስታ ድባብ ውስጥ አዲስ ነገሮች ለማየት የሚጠቅሙ ሶስት መርሆችን ልጥቀስና የዛሬውን ፅሁፌን ልጠቅልል።
​
  1. ትክክለኛ ጥያቄዎችን ደጋግሞ ራስን መጠየቅ። ​ለምሳሌ፦ “በኢትዮጵያ የተፈጠረው የዕድል መስኮት ለእኔ ምን ያስተምረኛል? ከእኔስ ምን ይጠበቃል?” ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል። “እስከ አሁን ከኖርኩበት የኑሮ እና የአስተሳሰብ ዘይቤ ምን ለውጥ ማድረግ አለብኝ?” ብሎ መጠየቅም ተገቢ ነው። “ምን አይነት ሽርክና ከማን ጋር መጀመር፤መቀጠል ወይም ማቆም አለብኝ?” ብሎ መጠየቅ አይከፋም። “በደጃፌ ለሚታዩ ችግሮች ምን መፍትሔ ማፍለቅ እችላላሁ?” ብሎ ማሰብ የአመራር ብስለት ነው።  
  2. ለአዲስ የወይን ጠጅ አዲስ አቁማዳ ማዘጋጀት ​ እንደ ቀድሞው እያሰብን የምንለውጠው ምንም ነገር የለም። ይህም ሲባል ትምህርት መማር የሚገባው መማር፣ የሚኖርበትን ክልል እና ብሔሩን ብቻ እያሰበ ሲኖር የነበረ ግለሰብ ሀገርን በሰፊው ለማወቅ ጥረት ማድረግ ከዚያ አልፎ ደግሞ ሀገርን ብቻ እያሰበ ከኢትዮጵያ ውጪ ምንም ያለ የማይመስለው ደግሞ አፍሪካን ለማወቅ (ከጫጉላ ሽርሽር ባለፈ) በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ጉብኝት ማድረግ። ይህ የዕድል መስኮት ትንሽ ለሚያስቡ የኃላ ኃላ ብዙም አይፈይድላቸውም። ተመልካች ብቻ ያደርጋቸዋል። የሚሰርቅም የነበረ እጁን ይሰብስብ። ንዴት፣ቁጣ፣ጥል እና ክርክር የሞላው በፍቅር ይሸነፍ፤ ስለፍቅርም ይቅር ይበል። በበቀል ውስጥ ያለ ልብ እና ዓይምሮ ዘመን ተሻጋሪ ራዕይ ማየት አይችልምና።
  3. ጊዜው አሁን ነውና ወደ ተግባር መግባት። ንግግራችን የትላንት ብቻ አይሁን። የትላንትም፥ የዛሬንም፥ የነገንም በአንድ ላይ እንቃኝ። “ለነገ አትጨነቁ” የሚለው ቅዱስ ቃል “አታስቡ፣አታቅዱ” አለመሆኑን የተረዳ ወደፊትን ያልማል። ከእግዚአብሄር ሃሳብ ጋር ራሱን ይቃኛል። እግዚአብሔር ዘንበል ባለበት በአሁኑ ጊዜ እንደ ኑኃሚን ወደ ሃገር ቤት የመመለስ ጊዜው አሁን ነው።አያሌ ቀናት ሲፀልዩ ለቆዩ ብዙ ነህምያዎች ወደ ሃገራቸው በዓላማ የመመለሻ ጊዜያቸው አሁን  ነው። ምን ትላላችሁ?​​

ተጨማሪ••• ከ habeshastudent.com የተወሰደ
ምን አልባት የምለው ነገር ግር ያላችሁ እና የህይወት ጎዳና መራራ ናት የምትሉ በአጠቃላይ በቤታችሁ ሰላም ለናፈቃችሁ ከመርሆዎች ሁሉ በፊት ቀዳሚ የሆነውን የሰላም አለቃ ኢየሱስን ላስተዋውቃችሁ እወዳለሁ። 
​

ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ እንዲህ አለ፦ “ሰላምን እተውላችኃለሁ፣ ሰላሜን እሰጣችኃለሁ፤እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጣችሁ አይደለም፡፡ ልባችሁ አይጨነቅ አይፍራም፡፡” እንድንፈራ እንድንጨነቅ የሚያደርገን ከበቂ በላይ የሆነ ምክንያት ሊኖረን ይችላል፤ ነገር ግን እግዚአብሔር በፊታችን ካለው ችግር የሚበልጥ ሰላምን ይሰጠናል፡፡ እርሱ ከሁሉ በላይ የሆነ ፈጣሪ እግዚአብሔር(አምላክ) ነው፤ እርሱ ለዘላለም ይኖራል፤ ፍጥረተ አለምን ሁሉ የፈጠረ ከሁሉ ነገር ጀርባ ሆኖ የሚቆጣጠር እርሱ ነው፡፡

ይህን ሁሉ ኃያልነቱን ይዞ፣ እኛን እያንዳንዳችንን በጥልቀት ያውቀናል፤ በጣም ኢምንትና አናሳ የሆኑ ዝርዝር ጉዳዮቻችንን ሁሉ ያውቃል፡፡ በሕይወታችን በሚገጥመን ነገሮች ሁሉ በእርሱ ብንታመን፣ ራሳችንንም በእርሱ ላይ ብናሳርፍ፣ ምንም እንኳን ከፈተናና ከችግሮች ጋር ብንጋፈጥም ያለ አንዳች ጉዳት እርሱ ይዞ ያሳልፈናል፡፡ ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ “በእኔ ሰላም እንዲኖራችሁ፣ ይህንን ነግሬአችኋለሁ፡፡ በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ፡፡” እርሱ የሁሉ የመከራ ቁንጮ በሆነው ሞት ውስጥ አልፎ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል፡፡ በእርሱ የምንታመን ከሆነ በሕይወታችን በሚገጥሙን አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እጃችንን ይዞ ይመራናል። ከሁሉም በላይ ደግሞ እርሱ ከሞት እንደተነሳ ሁሉ በመጨረሻው ቀን በእርሱ የምናምን እኛን ከሞት እንደሚያስነሳንና ወደ ዘላለም ሕይወትም እንደሚወስደን ቃል ገብቶልናል፡፡ ኢየሱስን የበለጠ ለማወቅ ይህን ድህረ ገፅ ይክፈቱ። 

Comments are closed.

    Author

    Miheret T. Eshete 
    I am passionate about making Jesus known to all cultures and people groups in the world. 
    Read more about my childhood story here. 

    View my profile on LinkedIn

    Archives

    February 2023
    November 2021
    July 2021
    April 2021
    October 2020
    September 2020
    August 2020
    March 2020
    January 2020
    November 2019
    October 2019
    July 2019
    June 2019
    March 2019
    February 2019
    November 2018
    July 2018
    November 2017
    October 2017
    September 2017
    August 2017
    July 2017
    June 2017
    May 2017
    April 2017
    March 2017
    February 2017
    January 2017
    December 2016
    October 2016
    September 2016
    August 2016
    May 2016
    February 2016
    January 2016
    December 2015
    October 2014
    March 2014
    October 2013
    January 2011

    Categories

    All
    Africa
    Church
    Digital Mission
    Ethiopia
    Facebook
    Family
    Indigitous
    Interview
    Mission
    Missionary Life Style
    Mobile
    My Story
    Newsletter
    SMS
    Social Media
    Travel

    RSS Feed

  • Home
  • Blog
  • Give
  • About